አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዓለም የማይዳሰስ ቅርስነት የተመዘገበውን የጥምቀት በዓል ለማክበር ዝግጅት መደረጉን የጎንደር ከተማ አስተዳደር አስታውቋል፡፡
በዓሉ ሀይማኖታዊና ትውፊታዊ ስርዓቱን ጠብቆ እንዲከበር ከማድረግ ጎን ለጎን ለከተማዋ ዘላቂ እድገት አስተዋጽኦ የሚኖራቸው የውይይት ፕሮግራሞች እንደሚኖሩ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ማስተዋል ስዩም ተናግረዋል፡፡