አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) 297 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ከሳኡዲ አረቢያ ወደ አገራቸው መመለሳቸው ተገለፀ፡፡
ዛሬ ወደ አገራቸው ከተመለሱት 297 ኢትዮጵያውያን ውስጥ 25ቱ ህጻናት መሆናቸው ታውቋል፡፡
ኢትዮጵያውያኑ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ሌሎች መስሪያ ቤቶች የተወከሉ ሃላፊዎች አቀባበል እንዳደረጉላቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡