አዲስ አበባ፣ መስከረም 24፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሲጠበቅ የነበረውን የለንደን ማራቶን ኢትዮጵያዊው ሹራ ቅጣታ ቶላ ሲያሸንፍ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ ሲሳይ ለማ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቋል።
ሹራ ቅጣታ ቶላ 2 ሰዓት ከ5 ደቂቃ ከ41 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው ውድድሩን ያሸነፈው።
ውድድሩን ሊያሸንፍ እንደሚችል በከፍተኛ ሁኔታ ሲጠበቅ የነበረው ኢሊውድ ኬፕቾጌ 8 ደረጃን በመያዝ አጠናቋል።
ኬንያዊው ቪንሴንት ኪፕቹምባ ሁለተኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀ ሲሆን ሌሎቹ ኢትዮጵያውያን ሞስነት ገረመው ፣ ሙሌ ዋሲሁን እና ታምራት ቶላ ከ4 እስከ 6ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል።