የሀገር ውስጥ ዜና

የአምቦ የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ግንባታ ዛሬም አልተጠናቀቀም

By Tibebu Kebede

December 19, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 9 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በ532 ሚሊየን ብር ወጪ ከ4 ዓመት በፊት የተጀመረው የአምቦ የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት መንገድ ግንባታ አሁንም አልተጠናቀቀም።

የከተማዋ ነዋሪዎች ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ባቀረቡት ቅሬታ፥ ለዓመታት የውስጥ ለውስጥ የአስፓልት ደረጃ መንገድ እንዲገነባ ሲጠየቅ ቢቆይም ፈጣን ምላሽ አለማግኘቱን አንስተዋል።