የሀገር ውስጥ ዜና

በቀጣይ ዓመት በ255 ሚሊየን ብር የ22 የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች የአዋጭነት ጥናትና ዝርዝር ዲዛይን ስራዎች እንደሚከናወኑ ተገለፀ

By Tibebu Kebede

August 25, 2020

አዲስ አበባ ፣ ነሀሴ 19 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ጥቅም ላይ መዋል የሚችሉ 22 መካከለኛና ትላልቅ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶችን የአዋጭነት ጥናትና ዝርዝር ዲዛይን ስራዎች እንዲሁም ክለሳ በ2013 በጀት ዓመት በማከናወን ለግንባታ ምቹ የማድረግ ስራዎች እንደሚከናወኑ ተገለፀ።

የሁሉም ፕሮጀክቶች የአዋጭነት ጥናትና ዝርዝር ዲዛይን ማከናወኛ 255 ሚሊየን ብር በጀት መያዙ ተነግሯል።