Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በክልሉ የተጀመሩ መሠረተ-ልማቶች ግንባታን በዚህ ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የተጀመሩ መሠረተ-ልማቶች ግንባታን በዚህ ዓመት መጨረሻ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተሠራ መሆኑን የሲዳማ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ደስታ ሌዳሞ ገለፁ፡፡

የክልሉ መንግሥት ለሕዝቡ የመሠረተ-ልማት ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እየሠራ መሆኑን ያነሱት አቶ ደስታ፤ በዚህም በበጀት ዓመቱ የተጀመሩ የውኃ፣ የመንገድና የድልድይ ግንባታዎች እየተፋጠኑ ነው ብለዋል፡፡

የመሠረተ-ልማቶቹ ን ግንባታ በበጀት ዓመቱ መጨረሻ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ለኢዜአ ተናግረዋል፡፡

የተጀመሩ የውኃ ፕሮጀክቶች የክልሉን የመጠጥ ውኃ ሽፋን ወደ 65 በመቶ ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት እንደሚያግዙም ነው ያመላከቱት፡፡

Exit mobile version