አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኦሮሚያ ክልል የኢንቨስትመንት ቦርድ 72 ቢሊየን ብር ላስመዘገቡ ከ2 ሺህ 500 በላይ ባለሃብቶች የመስሪያ ቦታ አስተላልፏል።
ቦርዱ በዛሬው ዕለት ባካሄደው ስብሰባ÷ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ባለሃብቶች እንዲሁም ግንባር ቀደም የሆኑ አርሶ አደሮች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ተቀባይነት ማግኘታቸውን የኦሮሚያ ክልል ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ አስታውቋል፡፡
በዚህም መሰረት 72 ቢሊየን ብር ካፒታል ላስመዘገቡ 2 ሺህ 500 ባለሃብቶች የኢንቨስመንት ፍቃድ መሰጠቱን የቢሮው ሃላፊ አህመድ ኢድሪስ ገልጸዋል።
ከ18 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ላይ ውሳኔ የተላለፈ ሲሆን÷ ኢንቨስተሮቹ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ወደ ሥራ እንደሚገቡ መገለጹን ከክልሉ ኢንቨስትመንት እና እንዱስትሪ ቢሮ የተገኘው መረጃ አመላክቷል፡፡