የሀገር ውስጥ ዜና

የዳቦ ስንዴን ከውጭ በግዥ የማስገባት ሂደት እየተከናወነ ነው

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች የሚታየውን የዳቦ ስንዴ እጥረት ለመቅረፍ መንግስት ስንዴን ከውጭ የማስገባቱን ሂደት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በኢትዮጵያ እየተመረተ ያለው የዳቦ ስንዴ ከፍላጎቱ ጋር ባለመጣጣሙ ምክንያት መንግስት ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በግዥ ከውጭ እያስገባ ይገኛል።