የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል ጓጉሳ ሽጉዳድ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ13 ሰዎች ሕይወት አለፈ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 6 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር በጓጉሳ ሽጉዳድ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ13 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የወረዳው ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጽህፈት ቤቱ ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አማረ ፈረደ ለአብመድ እንደተናገሩት፥ አደጋው ዛሬ ረፋድ 3 ሰዓት ላይ አዲስ ዓለም በምትባል የገጠር ከተማ አካባቢ የደረሰ ነው።