Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ማንቼስተር ዩናይትድ አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሃግን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ ዋና አሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሃግ ከኃላፊነታቸው ተሰናበቱ፡፡

በቀያይ ሰይጣኖቹ ቤት አሰልጣኝ ቴን ሃግ ስኬታማ ጉዞ እያደረጉ አይደለም በሚል ትችት ሲሠነዘርባቸው ቆይቷል፡፡

ቀያይ ሰይጣኖቹ ትናንት ባደረጉት የፕሪሚየር ሊጉ ዘጠነኛ ሣምንት ጨዋታ በዌስት ሃም 2 ለ 1 መሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

በክለቡ ቀደም ሲል በተጫዋችነት ከዚያም በምክትል አሰልጣኝነት ሲያገለግል የቆየው ሆላንዳዊው ሩድ ቫን ኒስተልሮይ በጊዜያዊነት ማንቼስተር ዩናይትድን በዋና አሰልጣኝነት እንዲመራ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

Exit mobile version