Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

4 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የዓመቱ ምርጥ አትሌት ዕጩ ውስጥ ተካተቱ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ዮሚፍ ቀጀልቻ፣ ታምራት ቶላ፣ ትዕግስት ከተማ እና ሱቱሜ አሰፋ የ2024 ከስታዲየም ውጭ የወንዶች የዓመቱ ምርጥ አትሌት ምርጫ ላይ በዕጩነት ተካተቱ፡፡

አትሌቶቹ በውድድር ዓመቱ በተለያዩ የጎዳና ላይ ውድድሮች ባስመዘገቡት ውጤት ነው ለዕጩነት መካተት የቻሉት።

በውድድር ዓመቱ አትሌት ታምራት ቶላ የኦሊምፒክ እና የበርሊን ማራቶንን ክብረ ወሰን በማሻሻል ጭምር ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

እንዲሁም አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቫሌንሺያ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር የዓለም ክብረ ወሰን በማስመዝገብ ማሸነፉ ይታወቃል፡፡

እንዲሁም በሴቶች አትሌት ትዕግስት ከተማ እና ሱቱሜ አሰፋ በዕጩነት መካተታቸውን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version