Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብና የምክክር ምዕራፍ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ምዕራፍ ሒደትን አስጀምሯል።

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)÷መሰረታዊ የሃሳብ ልዩነቶችና አለመግባባቶች እየሰፉ በመምጣታቸው ኮሚሽኑ እነዚህን ልዩነቶች በምክክር ለመፍታት ይቻል ዘንድ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልልም ለምክክር የሚቀርቡ አጀንዳዎች በውይይቱ እንደሚሰባሰቡ ጠቁመው÷ሒደቱ አሳታፊ፣ አካታችና ተዓማኒ እንደሚሆንም ተናግረዋል።

እስካሁን በ7 ክልሎችና 2 ከተማ አስተዳደሮች ከ932 ወረዳዎች የተውጣጡ 105 ሺህ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሒደቱ መሳተፋቸውን አንስተዋል፡፡

በአማራ እና ትግራይ ክልሎች የአጀንዳ ማሰባሰቡን ለማካሄድ ዝግጅቶች እየተደረጉ እንደሆነም ኮሚሽኑ አመላክቷል፡፡

በዘመን በየነ

Exit mobile version