Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የካፍ ልዑክ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎበኘ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ልዑክ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝታቸው ወቅት ልዑካኑ በሰጡት አስተያየት ÷የዓድዋ ድል ታሪክ በአፍሪካ ስርዓተ ትምህርት ውስጥ ሊካተት ይገባል ብለዋል፡፡

እንዲሁም በአፍሪካ የሚገኙ ታዳጊ ህፃናት እና ወጣቶች የነፃነት እና የሰው ልጆች እኩልነት ፈር ቀዳጅ የሆነችውን ኢትዮጵያን እና መታሰቢያውን እንዲጎበኙ ጥረት ሊደረግ ይገባል ማለታቸውን ከመታሰቢያ ሙዚየሙ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version