Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከ428 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ የኮንትሮባንድ እቃዎች ተያዙ

 

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ)የጉምሩክ ኮሚሽን ከጥቅምት 1 እስከ 7 ቀን 2017 ዓ.ም ባደረገው ክትትል ከ428 ሚሊየን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች መያዛቸው ተገለፀ፡፡

ከዚህም ውስጥ 134 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር የገቢ የኮንትሮባንድ እቃዎች ሲሆኑ÷ 294 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር የሚገመቱት ደግሞ የወጭ የኮንትሮባንድ እቃዎች መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ከተያዙት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ የግንባታ እቃዎች፣ ቡና፣ ጥራጥሬ፣ የተሽከርካሪ መለዋወጫ፣ የመዋቢያ እቃዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች ፣ መድኃኒት፣ የምግብ ዘይት ፣ የተለያዩ ተሽከርካሪዎች እና የውጭ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡

በተጠቀሰው ጊዜ የገቢ እና የወጭ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር ሀዋሳ፣ ሞያሌ እና ድሬድዋ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ቀዳሚውን ስፍራ እንደሚይዙ የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version