አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ፕሬዚዳንት ጆያኒ ቪንቼንዞ ኢንፋንቲኖ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ በአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) 46ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ ነው ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ የገቡት፡፡
ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር )፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጅራ አቀባበል አድርገውላቸዋል።