የሀገር ውስጥ ዜና

በመንግስት ሰራተኞች አዲሱ የደመዎዝ ጭማሪ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ውይይት ተካሄደ

By Melaku Gedif

October 21, 2024

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የመንግስት ሰራተኞች አዲሱ የደመዎዝ ጭማሪ አፈጻጸም መመሪያ ላይ ከክልልና ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊዎች ጋር ተወያይቷል፡፡

በውይይት መድረኩ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽነር መኩሪያ ሃይሌ (ዶ/ር)፣ የክልልና ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ሃላፊዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የመንግስት ሠራተኞች አዲሱ ደመዎዝ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡