Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አብርሆት የትውልዶችን ልቦና በእውቀት ለማብራት የተቋቋመ ነው- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 7፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) አብርሆት የትውልዶችን ልቦና በእውቀት ለማብራት የተቋቋመ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው÷አብርሆት የትውልዶችን ልቦና በእውቀት ለማብራት የተቋቋመ ነው ብለዋል፡፡

በሕንፃው ምሰሶዎች ጥበብ የሚለው ቃል በ18 የራሳቸው ፊደል ባላቸው ቋንቋዎች ተፅፎ የሚገኘውም ለዚህ ተልዕኮ ያለውን ቁርጠኝነት ለማመላከት ነው ሲሉ ገልጸዋል።

አብርሆት ቤተመፃህፍት በብልሃት ክህሎት የተጎናፀፉ ወጣቶችን የማብቃት አላማውን በትጋት በመወጣት ላይ ይገኛልም ነው ያሉት።

ዛሬ በአብርሆት ያገኘኋቸው ወጣቶች እንደ ሮቦቲክስ እና የፈጠራ ትግበራ ሥራዎች ላይ ተጠምደው ስላገኘኋቸው አድናቆት እና ማበረታቻ ይገባቸዋል ብለዋል።

መጪው ትውልድ ከኢትዮጰያ የልማት ግቦች ጋር በተናበበ ሁኔታ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በኮዲንግ፣ በሳይበር ሴኩሪቲ እና በመሳሰሉት ዘርፎች ክህሎታቸውን ማጠናከር መቀጠል እንደሚኖርባቸውም ገልጸዋል፡፡

Exit mobile version