Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሶማሌ ክልል የማህበረሰብ ወኪሎች የአጀንዳ ልየታ ምክክር መድረክ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 6፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሌ ክልል በሶስት ማዕከላት የተካሄደው የማህበረሰብ ወኪሎች የአጀንዳ ልየታ የምክክር መድረክ መጠናቀቁን የኢትዮጵ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የማህበረሰብ ክፍል ወኪሎች በ3 ማዕከላት ከወከሉት ማህበረሰብ ያመጧቸውን አጀንዳዎች አደራጅተው አጀንዳዎችን በአደራ ተረክበው ከባለ ድርሻ አካላት ጋር የሚመካከሩ ወኪሎችን መምረጣቸውን የኮሚሽኑ መረጃ አመልክቷል፡፡

Exit mobile version