Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

መልካ አቴቴ፣ መልካ ዶሻ እና መልካ ሰበታ የኢሬቻ በዓላት እየተከበሩ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2017 ዓ.ም የመልካ አቴቴ፣ መልካ ዶሻ እና መልካ ሰበታ ኢሬቻ በዓላት በተለያዩ አካባቢዎች እየተከበሩ ነው፡፡

በበዓላቱ አከባበር ላይ አባ ገዳዎች፣ ሀደ ሲንቄዎች፣ ቄሮዎች እና ቀሬዎችን ጨምሮ የየአካባቢዎቹ ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡

በዓላቱ እየተከበሩ የሚገኙት በአሰላ እና ሰበታ ሲሆን አከባበሩም ባህልና እሴቱን ጠብቆ እየተካነወ መሆኑ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ መልካ አሶሳ እየተከበረ መሆኑን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡

በሊያ ዱጉማ እና ፈጠነ ዘውዴ

 

 

Exit mobile version