Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በትራፊክ አደጋ የ2 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 27፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዳውሮ ዞን ሎማ ቦሳ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው ከኮንታ ዞን ጭዳ ወደ ወላይታ ሶዶ ሲጓዝ የነበረ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ በመገልበጡ ነው የደረሰው፡፡

በአደጋው የሁለት ሰዎች ሕይወት ያለፈ ሲሆን÷በሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ትናንት ምሽት 12 ሰዓት ላይ በደረሰው አደጋ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

Exit mobile version