Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አርባምንጭ ከተማን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡

በፕሪሚየር ሊጉ ሶስተኛ ሳምንት መርሐ ግብር 10 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አርባምንጭ ከተማ በድሬደዋ ስታዲየም ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡

ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁለት ጎሎችን ኪቲካ ጅማ፣ አንደኛዋን ጎል ደግሞ ፉዓድ ፈረጃ ሲያስቆጥር የአርባምንጭ ከተማን ብቸኛ ጎል አህብያ ብራያን አስቆጥሯል፡፡

Exit mobile version