Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ዓለም ባንክ የኢትዮጵያን የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ሂደት እደግፋለሁ አለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 22፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም ባንክ ኢትዮጵያ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገውን ሂደት በፋይናንስና በቴክኒክ እንደሚደግፍ አረጋገጠ፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ከዓለም ባንክ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት÷ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እያደረገች ያለውን ጥረት አብራርተዋል፡፡

የዓለም ባንክ የኢትዮጵያን ጥረት ሊደግፍ የሚችልባቸውን ጉዳዮች አመላክተው÷ ሂደቱ የሚቀላጠፍበት ሁኔታ እንዲፈጠር እግዛ እንዲያደርግ ጠይቀዋል፡፡

የባንኩ የሥራ ኃላፊዎች በበኩላቸው ኢትዮጵያ እያደረገች ያለውን ጥረትና ሂደት ባንኩ በፋይናንስና በቴክኒክ እንደሚደግፍ አረጋግጠዋል፡፡

Exit mobile version