Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሳሙኤል ኤቶ በፊፋ ቅጣት ተላለፈበት

አዲስ አበባ፣ መስከረም 20፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) ዲሲፕሊን ኮሚቴ በካሜሩን እግር ኳስ ማህበር ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ኤቶ ላይ ቅጣት መጣሉን አስታውቋል፡፡

የቀደሞ የባርሴሎና እና ኢንተርሚላን ኮከብ ቅጣት የተላለፈበት ያልተገባ ባህሪ በማሳየቱ እና የፊፋን ፍትሃዊ የጨዋታ መርሆች በመጣሱ ነው ተብሏል፡፡

ኤቶ ድርጊቱን የፈጸመው በኮሎምቢያ ቦጎታ በተካሄደው ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ዓለም ዋንጫ ብራዚል ከካሜሮን ባደረጉት ጨዋታ ወቅት መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በዚህም ኤቶ ለ6 ወራት ያህል የካሜሮን የሴቶች እና ወንዶች ብሄራዊ ቡድኖች በሚያደርጓቸው ጨዋታዎች እንዳይሳተፍ መታገዱን ፊፋ አስታውቋል፡፡

Exit mobile version