Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከንቲባ አዳነች አቤቤ 75 የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላለፉ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 19፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ ክፍለ ከተማ ባለ 5 ወለል 75 የመኖሪያ ቤቶችን ለነዋሪዎች አስተላለፉ፡፡

በዊንጌትና ገብስ-ተራ የቀበሌ ቤቶችን በማፍረስ ለመኖር ምቹ የሆኑ 75 የመኖሪያ ቤቶች ያላቸው ባለ 5 ወለል ሁለት ሕንጻዎችን በመገንባት ለነዋሪዎች ማስተላለፋቸውን ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

የመኖሪያ ቤቶቹ ከቦታው ከተነሱ ነዋሪዎች በተጨማሪ ለልማት ከመኖሪያ አካባቢያቸው ለሚነሱ ዜጎች የሚተርፉ ሆነው መገንባታቸውንም ገልጸዋል፡፡

ልማቱ ነዋሪዎችን የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ባለቤት እና ምቹ በሆኑ የመኖሪያ አካባቢዎች የመኖር ዕድልን የሚፈጥር መሆኑንም ነው የገለጹት፡፡

Exit mobile version