Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሲቲው አማካይ ሮድሪጎ ሄርናንዴዝ ከውድድር ዓመቱ ተሳትፎ ውጪ ሆነ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) ስፔናዊው የማንቼስተር ሲቲ አማካይ ሮድሪጎ ሄርናንዴዝ ባጋጠመው የጉልበት ጉዳት ከ2024/25 የውድድር ዓመት ተሳትፎ ውጪ መሆኑን ክለቡ አስታውቋል፡

ተጫዋቹ ጉዳቱን ያስተናገደው ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ከአርሰናል ጋር ባደረገው የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ላይ ነበር፡፡

የ28 ዓመቱ የዩሮ 2024 አሸናፊ ሮድሪ ማንቼስተር ሲቲ በቅርብ ዓመታት ላስመዘገበው ስኬት ቁልፉ ተጫዋች መሆኑ ይነገራል፡፡

ሮድሪጎ ሄርናንዴዝ የጉልበት ቀዶ ጥገና በስፔን ማድሪድ ማድረጉን ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል፡፡

ጉዳቱን ተከትሎም ሮድሪ ከውድድር ዓመቱ ተሳትፎ ውጪ መሆኑን የክለቡ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አስታውቀዋል፡፡

Exit mobile version