Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የመስቀል በዓል እየተከበረ ነው

 

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በመላ ሀገሪቱ እየተከበረ ይገኛል፡፡

በዓሉ በተለያዩ ሐይማኖታዊ እና ባህላዊ ሥነ-ሥርዓቶች ነው በድምቀት እየተከበረ የሚገኘው።

በትናንትናው ዕለት የመስቀል ደመራ በመላ ሀገሪቱ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት መከበሩ ይታወሳል፡፡

መስቀል ከቁሳዊ ይልቅ መንፈሳዊ ኃይል እንደሚበልጥ ማሳያ መሆኑን ትናንት በመስቀል ደመራ በዓል ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገልጸዋል፡፡

በዓለም ላይ እርስ በርስ አለመተማመን እንዲፈጠር ያደረገው በመስቀሉ ላይ የሚተላለፈው መልዕክት ገቢራዊ ባለመደረጉ መሆኑንም አንስተዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም ሕዝበ-ክርስቲያኑ እርስ በርስ በመደጋገፍ እና በመረዳዳት የመስቀል በዓልን ማክበር እንደሚገባው አስረድተዋል፡፡

 

Exit mobile version