Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የመስቀል ደመራ በዓል በመስቀል አደባባይ እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ መስከረም 16፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ እየተከበረ ይገኛል፡፡

በበዓሉ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፣ ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ፣ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካና ሚኒስትሮች እንዲሁም የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፣ አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶችን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት የመጡ ቱሪስቶች በበዓሉ ላይ ታድመዋል፡፡

በመርሐ-ግብሩ ሊቃውንተ-ቤተክርስቲያን ወረብ አቅርበዋል።

በመሳፍንት እያዩ

Exit mobile version