የሀገር ውስጥ ዜና

በሲዳማ ክልል የ2017 የትምህርት ዘመን ተጀመረ

By ዮሐንስ ደርበው

September 23, 2024

አዲስ አበባ፣ መስከረም 13፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሲዳማ ክልል የ2017 የትምህርት ዘመን መጀመሩን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

የክልሉ መንግሥት ለቅድመ መደበኛ ትምህርት ቅድሚያ ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን የቢሮው ምክትል ኃላፊ ሚሊዮን ዮሳ ገልጸዋል፡፡

ወላጆችም ልጆቻቸውን የመከታተል ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ኃላፊው መጠየቃቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡