Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አትሌት ሰውመሆን የመጀመሪያ ዙር የተሳካ የዓይን ቀዶ ጥገና አድርጓል- ፌደሬሽኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 11፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በልምምድ ላይ ሳለ በደረሰበት ጥቃት ግራ ዓይኑ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አጋጥሞት የነበረው አትሌት ሰውመሆን አንተነህ የመጀመሪያ ዙር የተሳካ የዓይን ቀዶ ጥገና ሕክምና ማድረጉን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አስታወቀ፡፡

ጉዳቱን ተከትሎ በሀገር ውስጥ ሕክምና ሲከታተል መቆየቱን እና ለተሻለ ሕክምና ወደ ሕንድ ቼይና ማቅናቱን ያስታወሰው ፌደሬሽኑ÷ አራት ሠዓታት የፈጀ የመጀመሪያ ዙር የተሳካ የዓይን ቀዶ ጥገና አድርጓል ብሏል፡፡

በአሁኑ ሠዓትም በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ እና ቀጣይ ሕክምናውን እየተከታተለ እንደሚገኝ መገለጹን የፌደሬሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version