A man holds a walkie talkie device after he removed the battery during the funeral of persons killed when hundreds of paging devices exploded in a deadly wave across Lebanon the previous day, in Beirut's southern suburbs on September 18, 2024. Hundreds of pagers used by Hezbollah members exploded across Lebanon on September 17, killing at least nine people and wounding around 2,800 in blasts the Iran-backed militant group blamed on Israel. (Photo by ANWAR AMRO / AFP)

ዓለምአቀፋዊ ዜና

በሂዝቦላህ ላይ የተፈጸመው የኤሌክትሮኒክስ ጥቃት በቀጣናው አዲስ ውጥረት መፍጠሩ ተገለጸ

By Mikias Ayele

September 19, 2024

አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሌባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሂዝቦላህ ላይ ያነጣጠረው የመገናኛ ሬዲዮ እና የኤሌክትሮኒክስ መሳሪዎች ጥቃት በመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና አዲስ ውጥረት መቀስቀሱ ተገልጿል፡፡

በሌባኖስ ፔጀርና ዎኪ ቶኪ የተሰኙ ሂዝቦላህ በብዛት የሚጠቀማቸው መገናኛ መሳሪያዎች መፈንዳታቸውን ተከትሎ ከ20 በላይ ሰዎች ሲሞቱ ከ3 ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

ከሞቱት ውስጥ ከ8 በላይ የሚሆኑት የሂዝቦላህ አባላት ሲሆኑ÷በሌባኖስ የኢራን አምባሳደር ሞይታባ አሚኒ በፍንዳታው አንድ አይናቸውን ማጣታቸው ተሰምቷል፡፡

በደህንነት ካሜራዎች የተቀረፁ ምስሎች በሌባኖስ፣ ሶሪያና ቤሩት በእንቅስቃሴ ላይ የነበሩ ሰዎች ሲጠቀሙባቸው የነበሩት የፔጀርና ወኪ ቶኪ መሳሪያዎች በድንገት ሲፈነዱ ያሳያሉ፡፡

ጥቃቱን  ፈጽማለች በሚል የተወነጀለችው እስራኤል እስካሁን ስለ ጉዳዩ ያለችው ነገር  አለመኖሩ የተመላከተ ሲሆን÷ ለአሜሪካ ግን በጥቃቱ ዙሪያ ገለጻ ማድረጓ ተጠቁሟል፡፡

በአንጻሩ የሌባኖስ የደህንነት ምንጮችየእስራኤሉ የስለላ ተቋም ሞሳድ በኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎቹ ላይ በቀላሉ የማይመረመር እና ኮድ የሚቀበል ፈንጅ ቀብሮ ነበር ሲሉ ወንጅለዋል፡፡

የምርቶቹ ባለቤት የሆነው የታይዋኑ ጎልድ አፖሎ ኩባንያ በበኩሉ ከፍንዳታው በስተጀርባ እጁ እንደሌለበት ገልጾ÷የፔጀርና ዎኪ ቶኪ ምርቶች መቀመጫውን ቡዳፔስት ባደረገው የቢኤሲ ኩባንያ የተመረቱ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ይሁን እንጂ ኩባንያው ይህን ያለው የሂዝቦላህን ቁጣ ለማብረድና የኤሌክትሮኒክስ ምርቶቹ ከገብያ እንዳይወጡ በመስጋት ነው መባሉን አረብ ኒውስ ዘግቧል፡፡