የሀገር ውስጥ ዜና

“የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ” እንዲቋቋም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ወሰነ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ”የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ” እንዲቋቋም ውሳኔ አሳለፈ።

የኤጀንሲው መቋቋም በተያዘው ዓመት በሰፊው የተሰራውን የትምህርት መሳሪያዎች አቅርቦትና የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብር ቀጣይነት እንዲኖረው እና ተቋማዊ ሆነው እንዲቀጥሉ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።