Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

1 ሺህ 34 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 4፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ 1ሺህ 34 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ተመላሾቹ 1 ሺህ 22 ወንዶች፣ 10 ሴቶችና 2 ጨቅላ ህፃናት ሲሆኑ÷ከእነዚህ መካከልም 26 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች እንደሚገኙ ተጠቁሟል፡፡

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ የማድረግና ከቤተሰብ ጋር የማቀላቀል ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡

Exit mobile version