የሀገር ውስጥ ዜና

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በመወያየት ውሳኔ አሳለፈ

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 77ኛ መደበኛ ጉባኤ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ በመወያየት ውሳኔ አሳለፈ።

ምክር ቤቱ የፌዴራል መንግስት ፕሮጀክቶች አስተዳደር እና አመራር ስርዓትን ለመደንገግ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቷል።