Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በፓራሊምፒክ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ በፓሪስ አቀባበል ተደረገለት

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ17ኛው የፓሪስ 2024 ፓራሊምፒክ ተሳታፊ የኢትዮጵያ የልዑካን ቡድን ደማቅ አቀባበል ተደረገለት።

የ33ኛው የፓሪስ ኦሊምፒክ ውድድር አካል የሆነው 17ኛው የፓራሊምፒክ ውድድር በፈረንጆቹ ከነሐሴ 28 እስከ መስከረም 8 ቀን 2024 ይካሄዳል፡፡

ኢትዮጵያን ወክሎ የሚሳተፈው ልዑክም ፓሪስ ሲደርስ በፈረንሳይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሀገሪቱ ከሚኖሩ የዳያስፖራ አባላት ጋር በመሆን ልዩ አቀባበል አድርገውለታል፡፡

በፓራሊምፒክ ውድድሩ ኢትዮጵያ በሁለቱም ጾታ እንደምትሳተፍ የኤምባሲው መረጃ አመላክቷል፡፡

Exit mobile version