የሀገር ውስጥ ዜና

በ2017 ዓ.ም የመልካም አስተዳደርና የጸጥታ ሥራዎች ላይ ትልቅ ለውጥ ለማምጣት ይሰራል – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ

By Melaku Gedif

August 08, 2024

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) መንግስት በ2017 በጀት ዓመት የመልካም አስተዳደር እንዲሁም የሰላምና ጸጥታ ሥራዎች ላይ ትልቅ ለውጥ ለማምጣት ይሰራል ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።

ተጠሪነታቸው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሆኑ አስፈጻሚ ተቋማት የ2016 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2017 ዕቅድ የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።

ውይይቱን የመሩት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጠሪ ተቋማት ለሌሎች ተቋማት አርዓያ የሚሆን ሥራ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል፡፡

አሁን ላይ የተጠሪ ተቋማቱ ሃላፊዎች የዝግጅት ምዕራፍ፣ የሥራ ትግበራና ውጤት እንዲሁም ፈተና በገለጻ እያቀረቡ ይገኛሉ።

በፍሬሕይወት ሰፊው