Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር በዛሬው ዕለት ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ ÷ በሚያዚያ ወር ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር በመገናኘት በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን አስታውሰዋል፡፡

በወቅቱም በየደረጃው ውይይቶች እንዲቀጥሉ አቅጣጫ ተቀምጦ እንደነበር ነው የገለጹት፡፡

ዛሬ የሚያዚያው ውይይት ቀጣይ የሆነና ሁሉን አቀፍ ጠቀሜታ ባላቸው ሀገራዊ ጉዳዮች መግባባት መፍጠርን የተመለከተ ውይይት መደረጉንም አስገንዝበዋል፡፡

Exit mobile version