Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ወደ ፓሪስ ለሚያቀናው የኢትዮጵያ ልዑክ በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት ከነገ በስቲያ ሽኝት ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2024 የፓሪስ ኦሎምፒክ ለሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 15 ቀን 2016 ዓ.ም በብሔራዊ ቤተ-መንግሥት የክብር ሽኝት እንደሚደረግ ተመላከተ፡፡

በሽኝት ሥነ-ሥርዓቱ ላይም ፕሬዚዳንት ሳኅለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች እንደሚገኙ መገለጹን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

በዚሁ ወቅትም የመልካም ምኞት መግለጫ መልዕክቶችና የሰንደቅ ዓላማ ርክክብ እንደሚኖር ተጠቁሟል፡፡

 

 

Exit mobile version