Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አርጀንቲና የኮፓ አሜሪካን ዋንጫ ለ16ኛ ጊዜ አነሳች

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) አርጀንቲና በኮፓ አሜሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ኮሎምቢያን በማሸነፍ ለ16ኛ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት ሆናለች፡፡

የሁለቱ ብሄራዊ ቡድኖች ጨዋታ በመደበኛ 90 ደቂቃ ያለ ግብ መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ ሰዓት አምርቷል፡፡

በዚህም ላውታሮ ማርቲኔዝ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ አርጀንቲና 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፋለች፡፡

ውጤቱን ተከትሎም አርጀንቲና የኮፓ አሜሪካን ዋንጫ ለ16ኛ ጊዜ አንስታለች፡፡

በጨዋታው ጉዳት አስተናግዶ ተቀይሮ የወጣው ሊዮኔል ሜሲ በሶስት ዓመታት ውስጥ አንድ የዓለም ዋንጫና ሁለት የኮፓ አሜሪካ ክብሮችን ከሀገሩ ጋር ማሳካት ችሏል፡፡

 

Exit mobile version