Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የ12 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እየተካሄደ ይገኛል።

የእቅድ አፈጻጸም ግምገማው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 4 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡

መድረኩ በበጀት ዓመቱ የተገኙ ስኬቶችንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ይገመግማል ተብሏል።

በተለይም የክልሉ መሰረታዊ ማነቆ የነበረው የሰላም እጦት በስፋትና በጥልቀት ውይይት እንደሚካሄድበት የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

ከዚህ ባሻገር በሌሎች ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና የመልካም አስተዳደር ዘርፎች ላይም ሪፖርት ቀርቦ ግምገማ እንደሚካሄድባቸው ይጠበቃል።

Exit mobile version