የሀገር ውስጥ ዜና

1 ሺህ 174 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

By Melaku Gedif

July 08, 2024

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በችግር ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 174 ኢትዮጵያውያን በዛሬው ዕለት ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ተመላሾቹ 1 ሺህ 095 ወንዶችና 79 ሴቶች ሲሆኑ÷ከእነዚህም መካከል እድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ 21 ታዳጊዎች ይገኙበታል።

ለተመላሽ ዜጎች ተገቢውን ድጋፍ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ሥራ በትኩረት እየተከናወነ እንደሚገኝም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡