አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ የዓለም የሰላም ኖቤል ተሸላሚ በመሆናቸው የደስታ መግለጫ መርሃ ግብር በተለያዩ ከተሞች ተካሄደ።
የደስታ መግለጫ መርሃ ግብሩ በዛሬው እለት ከማለዳው ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በጅማ፣ አዳማ፣ ቡራዩ፣ ሰበታ እና ቢሾፍቱ ከተሞች እንዲሁም በአማራ ክልል ባህርዳር ከተማ፣ በሀረሪ ክልል፣ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ፣ በሀዋሳ ከተማ እና በሌሎች ከተሞች ተካሂዷል።