የሀገር ውስጥ ዜና

በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ሕዝባዊ የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

By Mikias Ayele

July 07, 2024

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች “ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ ሐሳብ ሕዝባዊ የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

በዚህም አዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር፣ ማዕከላዊ ጎንደር፣ ደቡብ ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖችን ጨምሮ በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች የሰላም ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው፡፡