Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አለም አቀፍ የሐረር ቀንን በድምቀት ለማክበር ዝግጅት መደረጉ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 26ኛውን አለም አቀፍ የሐረር ቀን በሐረር ከተማ በድምቀት ለማክበር ዝግጅት መደረጉን የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦድሪን በድሪ አስታወቁ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ÷ 26ኛውን አለም አቀፍ የሐረር ቀን የሰላም ፣የፍቅርና የአብሮነት ከተማ በሆነችው ሐረር ከሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በታላቅ ድምቀት ለማክበር በቂ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

“ክብረ በዓሉ ህዝባችንን የሚያሰባስብና የሚያስተሳስር ከመሆኑም በላይ አብረን ለመልማትና ለማደግ የሚያስችል እንደሚሆን እምነቴ የፀና ነው” ሲሉም ነው የገለጹት።

Exit mobile version