Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴሬሽን ምክር ቤት 6ኛ የፓርላማ ዘመን፣ 3ኛ ዓመት የሥራ ጊዜ፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ፡፡

የተያዙ አጀንዳዎች በፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ከቀረቡ በኋላ ጉባኤው የቀረቡትን አጀንዳዎች መርምሮ በሙሉ ድምጽ በማፅደቅ ነው ጉባኤው መካሄድ የጀመረው፡፡

ምክር ቤቱ በመደበኛ ጉባኤው የ2016 ዓ.ም በጀት ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርትን ጨምሮ ለጉባኤው የተያዙ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችንና ቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version