Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የሱዊዝ ዲያግኖሲስ ማዕከልን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የሱዊዝ ዲያግኖሲስ ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በመዲናዋ የሚገኘውን የሱዊዝ ዲያግኖሲስ ማዕከል መጎብኘታቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ አስታውቀዋል፡፡

የሕክምና ማዕከሉ ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ባሻገር አዲስአበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን ራዕይ ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በቀጣይ በጤናው ዘርፍ የሚሳተፉ ሌሎች የግል ባለሃብቶችን በመደገፍ ከሀገር ወጥተው መታከም የማይችሉ ወገኖቻችን የተሻለ ሕክምና እንዲያገኙ እንዲሁም የውጪ ምንዛሬ ማስቀረት ላይ ጥረት ማድረጋችንን እንቀጥላለን ሲሉም ገልጸዋል፡፡

Exit mobile version