የሀገር ውስጥ ዜና

የዓለም የኖቤል የሰላም ሎሬት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

By Tibebu Kebede

December 17, 2019

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 2፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የኖቤል የሰላም ሎሬት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ማለዳ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ2019 የኖቤል የሰላም ተሸላሚ በመሆን ሽልማታቸውን ከትናንት በስቲያ በኖርዌይ ኦስሎ በተካሄደ ስነ ስርዓት መቀበላቸው ይታወሳል።