Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ ከቤላሩስ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮጵያ የቤላሩስ አምባሳደር ፓርቬል ቪዚያትኪ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ መደበኛ የፖለቲካ ምክክር በማካሄድ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል።

ኢትዮጵያና ቤላሩስ በኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ ግብርና፣ ትምህርት እና በአየር ትራንስፖርት ዘርፎች ያላቸውን ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መምከራቸውንም የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version