የሀገር ውስጥ ዜና

ቦርዱ የ6ኛው ዙር ቀሪ እና የድጋሚ ምርጫን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል

By ዮሐንስ ደርበው

June 21, 2024

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚያስፈጽመውን የ6ኛው ዙር ቀሪ እና የድጋሚ ምርጫን አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል፡፡

የመግለጫው ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚያስፈጽመውን የ6ኛው ዙር ቀሪ እና የድጋሚ ምርጫን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

ቦርዱ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. የ6ኛው ዙር ቀሪና እና የድጋሚ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ሂደትን እንደሚያስፈጽም ይታወቃል።

በዚህም መሠረት በዕለቱ የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን መስጠት እንዲችሉ፣ እንዲሁም የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወን ለማስቻል፣ ቦርዱ የሚከተሉትን ተግባራት ተፈጻሚ እንዲሆኑ “የምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የሥነ‐ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161” ላይ በተደነገገው የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ከታች የተዘረዘሩትን ተግባራት ያሳውቃል።

እንዲሁም እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ሰኔ 14 ቀን 2016 ዓ.ም.