Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአውሮፓ ዋንጫ ስፔን እና ጣልያን የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ ሁለተኛው ዙር የምድብ ማጣሪያ መርሐ ግብር ሶስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡

በዚህ መሰረትም በምድብ ሁለት የሚገኙት ጣልያን እና ስፔን ምሽት 4 ሰዓት ላይ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡

በመጀመሪያው የምድብ ማጣሪያ ጨዋታ ጣልያን አልባንያን 2 ለ 1 እንዲሁም ስፔን ክሮሺያን 3 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወሳል፡፡

በተመሳሳይ ምሽት 1 ሰዓት ላይ በምድብ ሶስት የሚገኙት እንግሊዝ እና ዴንማርክ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም ቀን 10 ሰዓት ላይ ከዚሁ ምድብ ስሎቬኒያ እና ሰሪቢያ ሁለተኛ ዙር የምድብ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

በምድቡ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ እንግሊዝ ሰርቢያን 1 ለ 0 ያሸነፈች ሲሆን፤ ዴንማርክና ስሎቬኒያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት መለያየታቸው ይታወሳል።

Exit mobile version