Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የግሪክ አምባሳደር አና ፋሩ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም አምባሳደር ምስጋኑ ÷ ኢትዮጵያና ግሪክ በህዝብ ለህዝብ፣ በኢኮኖሚያዊና ፓለቲካዊ መስኮች ያላቸውን ግንኙነት ማሳደግ እንዳለባቸው ገልጸዋል፡፡

ለዚህም በሁለቱ ሀገራት መካከል መደበኛ የፖለቲካ ምክክር ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።

በተጨማሪም ሁለቱ ወገኖች በሀገራቱ ግንኙነት ውስጥ መሻሻል ስላለባቸው ጉዳዮችና ስለ ሌሎች የሁለትዮሽ ጉዳዮች መምከራቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version